የክሽፈት እንጉርጉሮ፣ ታሪክ ላይ ተሸንቅሮ!

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክካሣሁን ዓለሙ

"አንድ ሰው በአደባባይ ሲናገርም ሆነ ጽሑፍ አሳትሞ ሲያሰራጭ ራሱን አጋልጦአል፤ የተናገረው ወይም የጻፈው መቶ በመቶ ያህል በራሱ ጉዳይ ላይ ብቻ ከሆነ፣ የመተቸት ወይም ሐሳብ የመስጠት ግደታ የለብንም፤ ነገር ግን የተናገረው ወይም የጻፈው በአገርና በሕዝብ ጉዳይ ላይ ከሆነ፣ የዚያ አገር ዜጋ ሁሉ በጉዳዩ ውስጥ የመሳተፍና ሐሳቡን በሙሉ ነጻነት የመስጠት መብት አለው።"

(ፕ/ር መስፍን ወልደማሪያም፣ መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ፣ ገጽ78-79)

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዶ/ር ጋሻው ስንኞች ከባህር ማዶ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Dr. Gashawዓለማየሁ ታዬ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

በያዝነው ዓመት የአማርኛ ቋንቋን የሥነ ግጥም እልፍኝ ካደመቋት አዳዲስ መድበሎች መካከል “ስንኞች ከባህር ማዶ” እጄ ገብታለች። በአንድ መቶ ሦስት ገጾች ተደጉሳ የሕትመት ብርሃን የሞቀችው ይህች መድበል 72 የአማርኛ እና ስምንት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ግጥሞችን ይዛለች። ገጣሚው በመግቢያው እንዳብራራው ግጥሞቹ የተጻፉት ባለፉት 38 ዓመታት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ በፕ/ር መስፍን ወልደማሪያም“ነፍስ ካለ፣ መፍጨርጨር አይቀርም!”

ሰሎሞን ተሰማ ጂ.

በሐምሌ 1955ዓ.ም የወጣው መነን መጽሔት፣ (7ኛ ዓመት፣ ቁ.10 ዕትም፣ በገጽ 27) ላይ እንዲህ የሚል ዘገባ አውጥቶ ነበር፤ “እኚህ የ33 ዓመት ወጣት በአባታቸው ጎንደሬ፣ በእናታቸውም ይፋቴ ሲሆኑ፣ በአማርኛ የበሰሉ በመሆናቸው የመናገርና የማስረዳት ስጦታ ያላቸው ትሁት ወጣት ናቸው፤” ሲል ይገለጻቸዋል። ለጥቆም የወጣቱን መስፍን ወልደ ማርያም ሦስት ሐሳቦች እንደሚከተለው አስፍሮት ይገኛል። “ማናችንም በዘመኑ የምንገኝ ትውልዶች በምናውቀውና በተማርነው ችሎታችን ተሽለን ተገኝተን፣ የዚህ ዕድል ተሣታፊ ለመሆን የሚጓጉ ወንድሞቻችንን ለመርዳት የምንቦዝንበት ትርፍ ጊዜ እንዲኖረን አያሻም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሥነ-ምግባር መሠረት - “ብፁዓን ንጹሓነ ልብ”

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ብፁዓን ንጹሓነ ልብ - እጓለ ገብረዮሐንስ (ዶ/ር)ሰሎሞን ተሰማ ጂ.

ያ ሰው ሞተ አሉኝ፣ እንዴት ያ ሰው ይሙት?

በሕይወት ሲያስተምር፣ ለሰው ልጆች ሕይወት፣

ተቀበረ አሉኝ፣ ከቶ እንዴት ይቀበር፣

ሙት ሕያው እንዲሆን፣ በቁሙ ሲያስተምር!

(“ስለ ክርስቲያን ሥነ-ምግባር መሠረት” (ብፁዓን ንጹሓነ ልብ)፤ ገጽ 165)

ከወራት በፊት “የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ” (ዘየአውዱት ከመ ዳመና)”ን ባወጣሁ ጊዜ እንደገለጽኩት፣ “የዶ/ር እጓለ ባለቤት ከባሕር ማዶ መጥተው፣ “የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ” የተባለውን መጽሐፍ በድጋሚ በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት እያሳተሙት መሆኑንና በቅርቡ እንደሚወጣም ጓደኛቸው ዶ/ር ምክረሥላሴ አበሰሩኝ ስል ጽፌ ነበር። በተጨማሪም፣ ደራሲው የአባታቸውን፣ የአለቃ ገብረ ዮሐንስ ተሰማንም ታሪክና ስራዎች የሚዘክር መጽሐፍም አዘጋጅተው ስላለፉ፣ እርሱም ጭምር ከላይ በተጠቀሰው ማተሚያ ቤት እየታተመ እንዳለና መገባደጃውም ላይ እንደሆነ” ዶ/ር ምክረሥላሴን በመጥቀስ ጽፌ እንደነበረ የሚታወስ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ታላላቅ የታሪክ ክህደቶች ከ“ፍኖተ ገድል”

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ፍኖተ-ገድልገብረመድህን አርአያ (ተጻፈ ሚያዝያ 6, 2004 ዓ.ም.)

ለአንድ ሰሞን ለአመታት በአሜሪካኗ ግዛት ኦሃዮ ውስጥ በስደት ሲኖር የነበረው የወያኔ ነባር ታጋይ፣ በስለላ የሰለጠነ … እና መሪህ ባኽታ ብስራት አማረ የጻፈው መጽሃፍ በህትመት ወጥቶ ጉድ፣ ጉድ ከተባለለት በኋላ እኔም እንደ ኢትዮጵያዊነቴ እና እንደ ቀድሞ የህወሃት ቀዳሚ ታጋይነቴ መጽሃፉን አግኝቼ ለማንበብ እና የግሌን ግምገማ ለማድረግ መፈለጌ አልቀረም። ዘግይቶም ቢሆን መጽሃፉ በእጄ ገብቶ የማንበብ እድል አገኘሁ። መቼም ጉድ ነው የሚባለው!! ህወሃት እና በዙሪያው የከበቡት ጉዶች የቅጥፈት እና የክህደት ጉድ ማለቂያ የለውም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ