የረቡዕ ግጥም ፪ኛ ዓመት፣ ፳፩
እናቴ ጭንቀትዋን መግለጽ ስትቸገር
ወልደህ እየው ብላ ትናገረኝ ነበር
ወልጄስ አየሁት ልክ ናት እናቴ
እንደምን ልውለዳት እንድትገባኝ ሚስቴ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





እናቴ ጭንቀትዋን መግለጽ ስትቸገር
ወልደህ እየው ብላ ትናገረኝ ነበር
ወልጄስ አየሁት ልክ ናት እናቴ
እንደምን ልውለዳት እንድትገባኝ ሚስቴ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ዛሬ ጊዜ ሰጥቶህ እኔን ብታጠፋ
አታመልጥም አንተም ከመሞት ወረፋ
ያተረፍከው ሲታይ ኋላ ተጠቃሎ
መብለጥህ ብቻ ነው በክፋትህ ኪሎ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





መተካት ቢችልም ሰውን ሰው አፍርቶ
ዓለም ተለውጧል የድሮ ሰው ጠፍቶ
መሠልጠን ነው ካልነው አዎ ሠልጥነናል
ያንኑ ያህል ግን ሰውነት አጥተናል
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ጉድ ብለን ነበረ በጃንሆይ እስር
ታላቅ መንግሥታቸው በደርግ ሲደፈር
ደርግም ተወራጭቶ ብን ብሎ ጠፋ
የዚህኛው ታየኝ ከሁሉም ሲከፋ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ከወደድነው እንጂ አብረን ከጠላነው
ቀጥ ያለው ጠማማ ጣፋጩም ሬት ነው
ፊልተር የመሰለው ጥርት ያለው ጠላ
የተበጠበጠ ይባላል አተላ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5





አንተን ጌታ ሲፈጥር
እሱን ጌታ ሲፈጥር
ትልቅ ነው ትንሽ ነህ
አላለህም ነበር
ከሱ በታች አ’ርጋ
ያዋለችህን ሆድ
ባቅምህ ድፈንና
ውጣ ከመዋረድ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5





ሲበሉ ካልበሉ ሲጠጡ ካልጠጡ
ከሰው ካልወሰዱ የጅዎን ካልሰጡ
ወይም ካልጎተቱ ወይ ካልተጎተቱ
ካላስፈተፈቱ ወይ ካልፈተፈቱ
ወይም ካልደለቁ ወይ ካላዳለቁ
እንኳንስ አኩርፈው ቢስቁም አይደምቁ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5





እንደናቴ የሚተወኝ
በጥፋቴ የማይወቅሰኝ
በይቅርታ የሚዘለኝ
ማን ሊመጣ ወዴት ሊገኝ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5





ልጅነቴን እንግልት
ወጣትነቴን ዕንክርት
ጉልምስናዬን ፍርሃት
ጋጥ አድርጎ እንክት አድርጎት
በባዶ አካል በባዶ ቤት
አሳዘነኝ መምጣቱ ሞት
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ቢገድሉና ቢያስሩን ምንም ቢያሰቃዩን
ጠፍተን አንጠፋም አይዞሽ እንድናለን
የትውልዱ ሕይወት ፈክቶ የሚያብበው
በደማችን ፍሳሽ በስጋችን ፍግ ነው
ሙሉውን አስነብበኝ ...