የቅንጅት አመራርን ለማስማማት የተሰባሰቡ 2 ለ15 ልዩነት ፈጠሩ

"ኢ/ር ኃይሉ በሌሉበት መነጋገር አንችልም" የአቶ አባይነህ ቡድን

"ኢ/ር ኃይሉ ሻውል የሚመጡበትን ቁርጥ ቀን ንገሩንና እናራዝመው ..." እነ ወ/ት ብርቱካን

"ኢ/ር ኃይሉ ሻውል በሦስት ምክንያቶች ቶሎ ወደ ኢትዮጵያ አይመለሱም፤ አንደኛው የጤናቸው ሁኔታ ነው፣ ሁለተኛው ደግሞ አሜሪካን ሀገር ባሉት አባላት መካከል ብዙ የተበላሹ ነገሮች ስላሉ እሱን ለማስተካከል ሲሆን ሦስተኛው ከግል ሕይወታቸው ጋር የተያያዘ መሆኑ ..." የኢንጂንየር ኃይሉ ባለቤት

ሪፖርታዥ

Ethiopia Zare (ዓርብ የካቲት 14 ቀን 2000 ዓ.ም. February 22, 2008)፦ ከእስር የተፈቱት የቀድሞው ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አመራሮችን በጋራ አሰባስቦ እንዲነጋገሩ ለማድረግና ድርጅቱን እንደ ድርጅት ለማስቀጠል ጥረት ሲያደርግ የነበረው 17 አባላት ያሉት የሽማግሌዎች ስብስብ በመጨረሻ ባወጣው መግለጫ ሁለት ለ 15 ልዩነት የፈጠሩ መሆናቸውንና አብዛኞቹ ለሽምግልናው አለመሳካት መንስኤው ኢ/ር ኃይሉ ሻወል መሆናቸውን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ክፍሌ ጥግነህ በአሜሪካ የድጋፍ ሰጪዎች ቦርድ ሊያስመርጡ ነው

Ethiopia Zare (ቅዳሜ የካቲት 8 ቀን 2000 ዓ.ም. February 16,2008)፦ የሰሜን አሜሪካ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ድጋፍ ሰጪዎች ማኅበር በሚያደርገው የቦርድ ምርጫ አቶ ክፍሌ ጥግነህ ተገኝተው ሊያስመርጡ መሆኑን አንድ ዘገባ ጠቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአዲስ አበባ ከፍተኛ የትራንስፖርት እጥረት ተከሰተ

አንበሣ አውቶቡስ ዋጋ ጨመረ

Ethiopia Zare (ዓርብ የካቲት 7 ቀን 2000 ዓ.ም. February 15,2008)፦ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለውን የአዲስ አበባን ነዋሪን ገቢ ባላገናዘበ መልኩ የአንበሣ አውቶቡስ ከ25 እስከ 50 ሣንቲም የታሪፍ ጭማሪ በማድረጉ የከተማው ነዋሪ በከፍተኛ ሁኔታ መማረሩ ተደመጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፎቶ ጋዜጠኞች ማኅበር ተቋቋመ

Ethiopia Zare (ዓርብ የካቲት 7 ቀን 2000 ዓ.ም. February 15,2008)፦ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የፎቶ ጋዜጠኞች ማኅበር በዚህ ሣምንት መቋቋሙ ታወቀ። የማኅበሩ መጠሪያ ስም "ብሔራዊ የፎቶ ጋዜጠኞች ማኅበር" ሲሆን፣ ፕሬዝዳንቱ አቶ ቢንያም መንገሻ መሆናቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቅንጅት ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ ተቀማ

አከራዮቹን ደህንነቶች እያስፈራሩ ነው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ የካቲት 4 ቀን 2000 ዓ.ም Feb. 12,2008)፦ በምክትል ሊቀመንበሯ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የቅንጅት ሥራ አስፈጻሚ በአንድ የሕግ ባለሙያ አማካኝነት የተከራዩትን ቢሮ የቤቱ ባለቤትና አከራይ የወያኔ ደህንነቶችና የቀበሌ ደንብ አስከባሪዎች ለሕገወጥ ተግባር ቤቱን አከራይተሻል በሚል ጫና በማሳደራቸው ምክንያት በዛሬው ዕለት አስለቅቃቸዋለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

26 የቅንጅት እስረኞች ዛሬ ተለቀቁ

የተፈቱ እስረኞችን ስም ዝርዝር ይዘናል

Ethiopia Zare (አርብ ጥር 30 ቀን 2000 ዓም. Feb.8,2008):- በቅንጅት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ጥረት ከምርጫ 97 ጋር በተያያዘ ለ30 ወራት በእስር ተጥለው የቆዩት የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ አባላትና ደጋፊዎች ዛሬ ከሰአት በኋላ መለቀቃቸውን ታማኝ ምንጮቻችን ዘገቡ። እስረኞቹ የተፈቱት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው እስረኞችን ለማስፈታት ባዋቀረውና በወ/ት ብርቱካን የሚመራው ንኡስ ኮሚቴ ከሽማግሌዎች ጋር ባደረጉት ጥረት መሆኑን ለማወቅ ችለናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለሁለት ጋዜጠኞች የአሣታሚነት ፈቃድ ተሰጠ

ሦስት ጋዜጠኞች ግን እንደተከለከሉ ነው

Ethiopia Zare (ኀሙስ ጥር 29 ቀን 2000 ዓ.ም. February 7,2008)፦ የጋዜጣ አሣታሚነት ፈቃድ ተከልክለው ከነበሩት አምስት ጋዜጠኞች ውስጥ ለሁለቱ በትናንትናው እና በዛሬው ዕለት ከረዥም ጊዜ መጉላላት በኋላ እንደተሰጣቸው ለማወቅ ችለናል።

‹‹መንግስት ሊያስጨርሰን ዝም ብሎ እያየን ነው›› የደብረሊባኖስ ገዳም መነኮሳት

በአካባቢው የጎሣ ችግር እንዳይከሰት ተሰግቷል

ልዩ ሪፖርታዥ

Debre Libanos MonasteryEthiopia Zare (ማክሰኞ ጥር 27 ቀን 2000 ዓ.ም. February 5,2008):- ለ838 ዓመታት በታሪካዊ ገዳምነት የሚታወቀው የደብረ ሊባኖስ ገዳም አካባቢ ወደ ቀበሌነት መለወጥን የተቃወሙ መነኮሳት፤ የገዳሙ ወደ ቀበሌነት መለወጥ የኃይማኖታዊ ተግባሩ ጋር በፍጹም የሚቃረን ነው ሲሉ አቤቱታቸውን ለማሰማት ወደ ፓትሪያርኩ ቢሮ መምጣታቸውንና በእንግልት ላይ መሆናቸውን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ጠቆመ። ከአዲስ አበባ የደረሰን ሪፖርት እንዲህ ተዘግቧል፦

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የላዕላይ ምክር ቤቱ አባላት አሰላለፍ ዝርዝር ታወቀ

አዲስ የተመረጡ የላዕላይ ምክር ቤት አባላት ዝርዝር

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥር 26 ቀን 2000 ዓ.ም. February, 4,2008)፦ ስድሳ አባላትን ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረው የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አመራሮቹ ከተፈቱ በኋላ ይፋ በሆነው አለመግባባት የላዕላይ ምክር ቤቱ አባላት በስድስት የተለያዩ አሰላለፍ ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ በአብዛኛው በተቀዳሚ ም/ሊቀመንበሯ የሚመራውን የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አሰላለፍ የሚደግፉ መሆኑ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...