የቅንጅት አመራርን ለማስማማት የተሰባሰቡ 2 ለ15 ልዩነት ፈጠሩ
"ኢ/ር ኃይሉ በሌሉበት መነጋገር አንችልም" የአቶ አባይነህ ቡድን
"ኢ/ር ኃይሉ ሻውል የሚመጡበትን ቁርጥ ቀን ንገሩንና እናራዝመው ..." እነ ወ/ት ብርቱካን
"ኢ/ር ኃይሉ ሻውል በሦስት ምክንያቶች ቶሎ ወደ ኢትዮጵያ አይመለሱም፤ አንደኛው የጤናቸው ሁኔታ ነው፣ ሁለተኛው ደግሞ አሜሪካን ሀገር ባሉት አባላት መካከል ብዙ የተበላሹ ነገሮች ስላሉ እሱን ለማስተካከል ሲሆን ሦስተኛው ከግል ሕይወታቸው ጋር የተያያዘ መሆኑ ..." የኢንጂንየር ኃይሉ ባለቤት
ሪፖርታዥ
Ethiopia Zare (ዓርብ የካቲት 14 ቀን 2000 ዓ.ም. February 22, 2008)፦ ከእስር የተፈቱት የቀድሞው ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አመራሮችን በጋራ አሰባስቦ እንዲነጋገሩ ለማድረግና ድርጅቱን እንደ ድርጅት ለማስቀጠል ጥረት ሲያደርግ የነበረው 17 አባላት ያሉት የሽማግሌዎች ስብስብ በመጨረሻ ባወጣው መግለጫ ሁለት ለ 15 ልዩነት የፈጠሩ መሆናቸውንና አብዛኞቹ ለሽምግልናው አለመሳካት መንስኤው ኢ/ር ኃይሉ ሻወል መሆናቸውን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ አስረዳ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
Ethiopia Zare


