የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ መግለጫ

TPLF

ጥቅምት 4 ቀን 2012

የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ከመስከረም 26 እስከ ጥቅምት 2/ 2012 ዓ/ም ድረስ ለተከታታይ 7 ቀናት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በ2011 ዓ/ም ተይዘው የነበሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅዶች፤ ድርጅታዊና ፖለቲካዊ ስራዎች በተለይ ደግሞ በአዲሱ የፖለቲካ መድረክ የትግራይ ሕዝብ ህልውና፣ ደህንነትና ዋስትና ለማስጠበቅ የተካሄደ ሁለንተናዊ የመመከት ትግል እና ይህንን መሰረት በማድረግ የተሰሩ ስራዎች በዝርዝር ገምግሟል። በዚህ ልዩ የትግል ምዕራፍ የታዩ ጥንካሬዎችንና ጉድለቶችን በመገምገም ሊወሰድ የሚችል ትምህርት በመለየት በዚህ ዓመት ሊሰሩ የሚገባቸው ልማታዊና ፖለቲካዊ እቅዶችንም አጽድቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የኢትዮጵያ ሕዝብ የፍትሕና የነፃነት ጥያቄ በግዴለሽነት በሚንቀሳቀሱ ሰዎችና ተግባራቸው እንዳይታጠፍ ሁሉም ዘብ ሊቆም ይገባል” ኢዜማ

Ethiopian Citizens for Social Justice Party (E-Zema)

ማክሰኞ መስከረም ፳፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. October 8, 2019፣ “የኢትዮጵያ ሕዝብ የፍትሕና የነፃነት ጥያቄ በግዴለሽነት በሚንቀሳቀሱ ሰዎችና ተግባራቸው እንዳይታጠፍ ሁሉም ዘብ ሊቆም ይገባል” በሚል ርዕስ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ - ፍትሕ ፓርቲ (ኢዜማ) መግለጫ አወጣ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕዝብ ተሳትፎ የሌለበት ውሳኔ፤ መፍትሔ አያመጣም (ሸንጎ)

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)

ሚዳቋ ወዲህ፤ ቅዝምዝም ወዲያ እንዲል ያገራችን ሰው፤ የሰሞኑ የኢሕአዴግ መንግሥት አካሄድም ከሕዝብ ፍላጎትና ከሕዝብ ጥያቄ ጎን ሲለካ ወዲያና ወዲህ ሆኖ አግኝተነዋል። ሕዝብ የሚጠይቀውና የሚፈልገው አንድ ነገር፤ መንግሥት አደርጋለሁ የሚለው ሌላ ነገር። ይህም በተለይ ባለፈው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁለት ዐበይት ጉዳዮች ላይ ያሰሙትን መግለጫ ይመለከታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአልጀርስ ስምምነትና የድንበር ኮሚሽኑ ውሳኔ ውድቅ ይደረጉ፤ የመለስ ተከታዮች ከሥልጣን ይወገዱ

የኢትዮጵያውያን ተጋሩ የውይይት መድረክ

በቅርቡ የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያን ሕዝብ ጥቅምና ክብር አሳልፎ የሰጠውን የአልጀርስ ስምምነትና የድምበር ኮሚሽኑን ፍርደ-ገምድል ውሳኔ ሙሉ በሙሉ ተቀብሎ እንደሚተገብረው አሳውቋል። ኢትዮጵያ ከድል መንጋጋ ሽንፈትን መንጭቃ አወጣች እንደተባለው ከበርካታ መሥዋእትነት በኋላ ለምን ወደ ድርድር ተሂዶ መራራ ዲፕሎማሲያዊ ሽንፈት ማምጣት እንዳስፈለገ በውል ባይታወቅም፣ ከዚያም በኋላ የአልጀርስ ስምምነት ውድቅ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊና ሕጋዊ ምክንያቶች እያሉ ለምን በአጣዳፊና ግብታዊ በሆነ መንገድ ውሳኔውን ተቀብለናል ማለት እንዳስፈለገ ግልጽ አይደለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር የ”አልጀርሱ ውል”ን ይቃወማል!

TAND

ጥናታዊ -ምክክር እንዲደረግ ይጠይቃል

የኢትዮጵያና የኤርትራ ድንበርን አስመልክቶ ከ16 ዓመታት በፊት በአልጀርስ የተፈጸመው ደባ በሁለት ዲክታተሮች መካከል የተደረሰ ስምምነት እንጂ፤ ሕዝቦቻችንን እንደማይወክል ከዚህ በፊት ደጋግመን ግልጽ አድርገናል። ይህ ሕዝቦቻችንን የማይወክል የ”አልጀርሱ ውል” እንዳለ አሁን በዶ/ር ዐቢይ የሚመራው መንግሥት ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩ ስንሰማ ከልብ አዝነናል። እንድንቃወምም ግድ ሆኖብናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ትግራዋይ መበለጥን አይፈልግም፣ ትግራዋይ ለአማራ፣ ለኦሮሞ፣ ለሶማሌ ሊጠረጥርና ሊያጎነብስ ነውር ነው” - ጌታቸው ረዳ

ጌታቸው ረዳ

“ከሁሉም ነገር በላይ ግን ትግራዋይ እየተሸነፍኩ ነው የሚል እሳቤ ለአማራ ሊጠረጥርና ሊያጎነብስ፣ ለኦሮሞ ሊጠረጥርና ሊያጎነበስ፣ እንደ ሕዝብ ለሶማሌ ሊጠረጥርና ሊያጎነብስ ነውር ነው! ይህ በትግራዋይ ታሪክ አልነበረም!!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለአቶ አባይ ፀሐዬ የተሰጠ ምላሽ፣ ከትዴት

Abay Tsehaye

ወርቅና ሐቅ እያደረ ይጠራል

ትዴት (የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ትብብር)

ሕወሓት በመላው ኢትዮጵያ እየተደረገበት ባለው ትግልና ጫና ተገዶ፣ እንደዚሁም በኢህአዴግ ራሱ ውስጥ ባሉት ፓርቲዎች መካከልም በተፈጠረው ፉክክርና ፍትጊያ የተነሣ ምስጢር አድርጎ ደብቆት የነበረውን ሐሰትና ማወናበድን አንድ ባንድ እያለ እያጋለጠው ይገኛል። ይህ ሁኔታ እዚህ ላይ የሚቆም አይደለም፣ ሕዝቡ መብቱን ለማስከበር ቆርጦ ተነስተዋልና።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ