ስለ ግንቦት ሰባት፣ የሰባት መቶ ሰባ ሰባት አስተያየቶች መባቻ (አባኪያ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ከአባኪያ

እንደመግቢያ እንደመነሻ

ይሄንን ጽሁፍ እየጻፍኩ እያለ ጓደኞቼ የላኩልኝን በቻይና ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት ለማቋቋም ሲሞክር ስለታሰረ ሰውና እየተመላለሰች ስለምትጠይቀው እህቱ የሚያትት ጽሑፍ ሳነብ፣ የሚማርክና ከኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር የሚመሳሰል ሃሳብ አገኘሁበትና እዚህች መጣጥፍ ላይ ሻጥ ላደርጋት አሰብኩ። ያው የቻይና መንግሥት ክስም እንደ ኢህአዴግ መንግሥት ክሶች ተመሳሳይ ነው። መንግሥት ለመገልበጥ ወይም ለመጣል አሲራችኋል አይነት ነገር። የጽሑፉ አቅራቢ ሴት፣ በዚህ ክስ የታሰረ ሕመምተኛ እስረኛ ወንድሟ በሕክምና አመክሮ ካገር ሊወጣ እንደሚችል የተሰጣትን ምክር ይዛ ምን እንደሚያስብ ብትጠይቀው፣ “I will not leave China unless my freedom of return is guaranteed” (ወደቻይና የመመለስ መብቴ ካልተረጋገጠልኝ በስተቀር አገሬን ለቅቄ አልሄድም) አላት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግንቦት ሰባት - ጉዳዩ ኢትዮጵያዊነት ነው (ግርማ ካሣ)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ግርማ ካሣ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

ትዝ ይለኛል በጥቅምት ወር 1984 ዓ.ም. አካባቢ ነበር፤ ሁለት ጓደኛምች በቸርችል ጎዳና፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ጀርባ በሚገኘው የ”ትግላችን” ኃውልት ጋር ፎቶግራፍ ለመነሳት የቆሙት። (ይህ ኃውልት አሁን ይኑር አይኑር አላውቅም) እነዚህ ወጣቶች፣ የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ምስል የሚታይበትን ኃውልት አክብረው ሳይሆን እዚያ ቦታ ፎቶግራፍ ለመነሳት የቆሙት፤ ከኃውልቱ በስተግራ በኩል መሬቱ ላይ ተተክለው የነበሩ አበባዎች ማርከዋቸው ስለነበር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የማሰር ባሕል (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

Prof. Mesfin Woldemariamመስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር) ግንቦት 2000

በጥንቶቹ መሣፍንት ዘመን፣ የአንድ ቡድን የሥራ መሪ ሆኜ ወደ ጎሐጽዮን ኼጄ ነበረ። የማላውቃቸው የወረዳው አስተዳዳሪ የሆኑ አንድ ባላምባራስ፣ መኪና ውስጥ ተቀምጬ ከሰው ጋር ስነጋገር አዩኝና አልወደዱልኝም። “ማነው ይኼ፣ ምንድነው የምታነጋግረው፣ …” እያሉ ሰውየውን ሲቆጡ፣ ከመኪና ወረድኩና ማንነቴን ገለጽኩላቸው፤ ደብዳቤም አሳየኋቸው። ከምመራው ቡድን ውስጥ አንድ አሜሪካዊ አይተዋልና መሪው እኔ ነኝ ስላቸው በጣም ተናደዱ። “ይኼ ደፋር! ፈረንጅ እያለ መሪው እኔ ነኝ ይላል?!” ብለው ወደ ፖሊሱ ዞሩና “ውሰደው፤ እሰርልኝ!” አሉት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቫቲካን ጥቅም ከኢትዮጵያ ክብር ይልቃል?!

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

(በኪዳኔ ዓለማየሁ)

ፋሺሽት ኢጣልያን ደግፋ ኢትዮጵያ ላይ ለደረሰው የሰው ዘር እልቂትና ሌላም ከባድ ጥፋት የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ በመደጋገም ተጽፎላት አሻፈረኝ ያለቺው የቫቲካን፤ ካቶሊካዊት መንግሥት፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በሰፊው ለመንቀሳቀስ (ለመዝመት ልበለው?) ቆርጣ የተነሳች መሆኑን የሚያመለክቱ ክስተቶች እየታዩ ነው። ለዚህም፤ 1ኛ/ በቫቲካን አማካኝነት አዲስ አበባ ሊከፈት ስለ ታሰበው ግዙፍ የሆነ የካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ እና 2ኛ/ ሰሞኑን ከፕሬዚዳንት ግርማ ጭምር ተገናኝተው ስለ ነበሩት፤ የቫቲካኑ መሪ ፖፕ ቤኔዲክት 16ኛ ልዩ ተወካይ፤ ካርዲናል ዲያስ፤ ኦፊሴልያዊ የኢትዮጵያ ጉብኝት በማስረጃነት መጥቀስ ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰው አገርን በመውረር ምን ይገኛል? (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

መስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር)

በዛሬው ጊዜ ዓለም አቀፍ ሕጎች፣ በተለያዩ የአካባቢ ማኅበሮችና በተባበሩት የዓለም መንግሥታት ማኅበር ታትመውና ታውጀው፣ ተሰብከው፣ ብዙ ዲስኩሮችም በታላላቅ ሰዎች በተደጋጋሚ ተደርጎባቸዋል። ከብዙ ዓመታት በፊት ቻይና ቲቤትን ስትውጥ፣ ለጥቂት ጊዜ ተወራና ተረስታ፤ እኛም ካልረሳነው ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ስትወር እንዲሁ ነበር፤ ዛሬ እኛም ወግ ደርሶን ከወራሪዎች ጋር መሰለፋችን በሰፊው እየተወራ ነው። አሁን ደግሞ የአውሮፓ ሕብረት “ቲቤት የቻይና አካል ነች” ብሎ ዐወጀ ይባላል። እንግዲህ ወረራ በይርጋ ይጸድቃል ማለት ነው፤ ጉልበተኞች ጨክነው ዘመናትን ካስቆጠሩ፣ ወረራው በይርጋ እንደሚጸናላቸው አዲስ ትምህርት እየተገኘ ነው። አሜሪካ በኢራቅ ስድስተኛ ዓመቱን እያስቆጠረ ነው፤ ስንት ዓመት ይቀረዋል? ሆኖም የአሜሪካ መንግሥት ከህዝብ ፈቃድ ውጭ ጉልበት የለውምና ወረራው በአሜሪካ ህዝብ ትዕዛዝ የሚያበቃበት ጊዜ ያለ ጥርጥር ይመጣል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...